BEGIN:VCALENDAR
VERSION:2.0
PRODID:-//Baltimore Selassie - ECPv6.1.3//NONSGML v1.0//EN
CALSCALE:GREGORIAN
METHOD:PUBLISH
X-WR-CALNAME:Baltimore Selassie
X-ORIGINAL-URL:https://www.baltimoreselassie.org
X-WR-CALDESC:Events for Baltimore Selassie
REFRESH-INTERVAL;VALUE=DURATION:PT1H
X-Robots-Tag:noindex
X-PUBLISHED-TTL:PT1H
BEGIN:VTIMEZONE
TZID:UTC
BEGIN:STANDARD
TZOFFSETFROM:+0000
TZOFFSETTO:+0000
TZNAME:UTC
DTSTART:20210101T000000
END:STANDARD
TZID:America/Halifax
BEGIN:DAYLIGHT
TZOFFSETFROM:-0400
TZOFFSETTO:-0300
TZNAME:ADT
DTSTART:20210314T060000
END:DAYLIGHT
BEGIN:STANDARD
TZOFFSETFROM:-0300
TZOFFSETTO:-0400
TZNAME:AST
DTSTART:20211107T050000
END:STANDARD
BEGIN:DAYLIGHT
TZOFFSETFROM:-0400
TZOFFSETTO:-0300
TZNAME:ADT
DTSTART:20220313T060000
END:DAYLIGHT
BEGIN:STANDARD
TZOFFSETFROM:-0300
TZOFFSETTO:-0400
TZNAME:AST
DTSTART:20221106T050000
END:STANDARD
TZID:America/New_York
BEGIN:DAYLIGHT
TZOFFSETFROM:-0500
TZOFFSETTO:-0400
TZNAME:EDT
DTSTART:20210314T070000
END:DAYLIGHT
BEGIN:STANDARD
TZOFFSETFROM:-0400
TZOFFSETTO:-0500
TZNAME:EST
DTSTART:20211107T060000
END:STANDARD
END:VTIMEZONE
BEGIN:VEVENT
DTSTART;TZID=UTC:20260118T010000
DTEND;TZID=UTC:20260120T110000
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20251230T033249Z
LAST-MODIFIED:20260118T002508Z
UID:2237-1768698000-1768906800@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ዓመታዊ የቅድስት ሥላሴ ፤ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት
DESCRIPTION:በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ወቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፤ ባልቲሞር ሜሪላንድ። \nእንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ። የልደት ፤ የቅድስት ሥላሴ ፤ የጥምቀትና  የቃና ዘገሊላ ዓመታዊ በዓላትን በጋራ እናክብር።
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8b%93%e1%88%98%e1%89%b3%e1%8b%8a-%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%8b%e1%89%b5/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;TZID=UTC:20260106T200000
DTEND;TZID=UTC:20260107T030000
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20260106T104040Z
LAST-MODIFIED:20260106T104040Z
UID:2262-1767729600-1767754800@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:የጌታቸንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል
DESCRIPTION:በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ወቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ፤ ባልቲሞር ሜሪላንድ። \nእንኳን ለጌታቸንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ። የጌታቸንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን በጋራ እናክብር።
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8b%a8%e1%8c%8c%e1%89%b3%e1%89%b8%e1%8a%95%e1%8a%93-%e1%8b%a8%e1%88%98%e1%8b%b5%e1%8a%83%e1%8a%92%e1%89%b3%e1%89%bd%e1%8a%95-%e1%8b%a8%e1%8a%a2%e1%8b%a8%e1%88%b1%e1%88%b5-%e1%8a%ad%e1%88%ad/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220819
DTEND;VALUE=DATE:20220820
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210628T174525Z
LAST-MODIFIED:20220330T104148Z
UID:1631-1660867200-1660953599@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ደብረ ታቦር
DESCRIPTION:ነሐሴ ፩፫ \nደብረ ታቦር ፣ ቡሄ ጌታ ብርሀነ መለኮቱን የገለጠበትን የምናከብርበት በዓል ነው። \nየዚህ በዓል መሠረት የክርስቲያን እምነት ሲሆን፣ ደብረ ታቦር በግዕዝ የታቦር ተራራ ማለት ነው፡፡ የታቦር ተራራ የሚገኘው አሁን ፍልስጥኤም ተብሎ በሚጠራው ሀገር ነው፡፡ ደብረ ታቦር ወይንም የታቦር ተራራ ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ደቀመዛሙርቱን ይዞ ወደ ተራራው የወጣበትና ፊቱ እንደፀሐይ የበራበት ልብሱም እንደብርሃን ነጭ የሆነበት ቦታ ነው፡፡ ይህ ቦታ ጌታ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ተራራ ነው። \nየማቴዎስ ወንገል ምዕራፍ ፲፯፦ ቁጥር ፩ እስከ ፭ ” ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ። እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።” \nዓቢይ መሠረቱ ይሄ ሲሆን፣ በአገራችን የክረምቱ አፈና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታየውም በዚህ በዓል አካባቢ ስለሆነ ይቺ ዕለት ‘ቡሄ’ የሚለውን ስያሜ አገኘች። ቡሄ ማለት ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡ \nበገጠርም ሆነ በየከተማው ልጆች ጅራፋቸውን ገምደው ሲያጮሁ (ሲያኖጉ) ይሰነብታሉ። እናቶችም ለበዓሉ ዝግጅት ስንዴ ሲለቅሙ፣ ሲፈትጉ፣ ሲፈጩ ይሰነብታሉ። ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት ጊዜው ምሽት ነበር፡፡ እረኞችም ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጡ፡፡ ታዲያ ያንን ማስታወሻ «ቡሄ» ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና ችቦ በማብራት በዓሉን የምናከብረውም ከዚህ በመነሣት ነው፡፡ \nየቡሄ ዜማዎች\nበዋዜማው የሠፈር ልጆች በየቤቱ እየዞሩ ሆያ ሆዬ! አሲዮ ቤሌማ እያሉ ይጨፍራሉ። \nቁጥር 1.\nቡሄ በሉ፣ ልጆች ሁሉ\nቡሄ መጣ፤ ያ መላጣ\nቅቤ ቀቡት፣ እንዳይነጣ \nክፈትልን በሩን\nየጌታዬን \nእዚያ ማዶ ነጭ ሻሽ\nእዚህ ማዶ ጥቁር ሻሽ\nየእኔማ ጌታ ነጭ ለባሽ። \nየወንዜው ነብር የወንዜው ነብር\nየኛማ ጌታ ሊሰጡን ነበር። \nሆይ ሾህዬ ሎሚታ\nልምጣ ወይ ወደማታ። \nለብሩ ነወይ ነወይ ሽጉዱ\nበአባትህ ጊዜ ሰንጋ ነው ልምዱ \nቁጥር 2\nቡሄ በሉ ! ሆ!\nቡሄ በሉ ! ሆ!\nያዳም ልጅ ሁሉ`! ሆ!\nየኛማ ጌታ ፣ የአለም ፈጣሪ\nየሰላም አምላክ፣ ትሁት መካሪ \nድምጽህን ሰማና በብሩህ ደመና\nየቡሄው ብርሃን ለኛ መጣና \nያዕቆብ ዮሃንስ ሆ! እንዲሁም ጴጥሮስ\nአምላክን አዩት ሆ! ሙሴ ኤልያስ\nአባቱም አለ ሆ! ልጄን ስሙት\nቃሌ ነውና ሆ! የወለለድኩት \nድምጽህን ሰማና በብሩህ ደመና\nየቡሄው ብርሃን ለኛ መጣና። \nቁጥር 3\nይሄ የንጋት ወጋገን ሲፈናጠቅ በጠዋት ውርጭ የሚዘመር ሲሆን በከባድ ድምጽና በጅራፍ ጩኸት የሚታጀብ፣ ስራዬ ተብሎ በገደላገደል ስር እንዲያስተጋባ ተደርጎ ብዛት ባላቸው ህጻናት በከፍተኛ ድምጽ የሚዘመር ነው። ሙሉ ዜማው ብዙ ቢሆንም በጥቂቱ እንዲህ ይላል \nቡሄ ና! ቡሄ\nቡሄ ና! ቡሄ\nአበባ ማለት ያደርሳል ካመት ( ጅራፍ ና ጥንጅት ድምጽ)\nኦሆ!\nቡሄ ቡሄ ና!\nቡሄ ቡሄ ና! \nቡሄ ና! ቡሄ!( የጥንጅትና የጅራፍ ድምጽ )\nቡሄ ና! ቡሄ! \nቁጥር 4\nለአባ ወራ\nመጣና መጣና ደጅ ልንጥና\nመጣና ባመቱ እንዴት ሰነበቱ፣\nክፈት በለዉ በሩን የጌታዪን\nክፈት በለዉ ተነሳ ያንን አንበሳ፣\nመጣሁኝ በዝና ተዉ ስጠኝ ምዘዝና\nየኔማ ጌታ የገደለበት\nስፍራዉ ጎድጉዶ ዉሃ ሞላበት\nእንኳን ሰዉና ወፍ አይዞርበት\nያሞራ ባልቴት ዉሃ ትቅዳበት።\nየኔማ ጌታ የሰጠኝ ካራ\nከዚህ ብመዘዉ ጎንደር አበራ፣\nየኔማ ጌታ የሰጠኝ ስንዴ\nገና ሳልበላዉ አበጠ ክንዴ።\nወይ የኔ ጌታ የሰጠኝ ሙክት\nእግንባሩ ላይ አለዉ ምልክት፣\nመስከረም ጠባ እሱን ሳነክት\nሆያ ሆዪ፣\nሆያ ሆዪ\nወይ የኔ ጌታ\nዋርካ ነህ ዋርካ\nቢጠለሉብህ የማታስነካ \nለእማ ወራ\nየኔማ እመቤት፣ እሜት እሜት\nሎሚ ተረከዝ ትርንጎ ባት\nየኔ እማ እመቤት የፈተለችዉ\nየሸረሪት ድር አስመሰለችዉ\nሸማኔ ጠፍት ማርያም ሰራችዉ\nለዝያች ለማርያም እዘኑላት\nአመት ከመንፈቅ ወሰደባት\nየኔማ እመቤት መጣንልሽ\nየቤት ባልትና ልናይልሽ።\nየኔማ እመቤት ብትሰራ ዶሮ\nሽታዉ ይጣራል ገመገም ዞሮ\nየኔማ እመቤት የጋገረችዉ\nየንብ እንጀራ አስመሰለችዉ።\n[1] \nበዚህ ጊዜ እናቶች ካዘጋጁት ዳቦ ይሰጧቸውና እየገመጡ ጅራፋቸውን ሲያጮሁ ያመሻሉ። የቡሄ ዕለት ለእያንዳንዱ የቤተሰብ፣ ዘመድ አዝማድ ልጅ አንዳንድ ሙልሙል ዳቦ በልጆቹ ልክ ይሰጣል። በቆሎ ተማሪዎች ዘንድ ደግሞ ደብረ ታቦር ‘የተማሪዎች በዓል’ ነው። ተማሪዎቹ ቀደም ብለው “ስለ ደብረ ታቦር” እያሉ እህሉንም፣ ብቅሉንም፣ ጌሾውንም ይለምኑና ጠላውን ጠምቀው፣ ዳቦውን ጋግረው፣ ቆሎውን ቆልተው ለደብረ ታቦር ዕለት ሊያስቀድሱ የመጡትን ምዕመናን ሁሉ ይጋብዛሉ። \nበአሁኑ ጊዜ፣ በተለይ በአዲስ አበባ ይሄንን መንፈሳዊና ባህላዊ መሠረት በመልቀቅ ለሕሙማን፣ አዛውንት እንዲሁም ለእንስሳት ድንጋጤ የሚፈጥረውንና ለእሳት አደጋ የሚያጋልጠውን ባእዳዊ ርችት በመተኮስ ሆኗል የሚከበረው። \n 
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8b%b0%e1%89%a5%e1%88%a8-%e1%89%b3%e1%89%a6%e1%88%ad/
ATTACH;FMTTYPE=image/png:https://www.baltimoreselassie.org/wp-content/uploads/2021/06/debretabor.png
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220612
DTEND;VALUE=DATE:20220613
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20220330T103901Z
LAST-MODIFIED:20220330T133020Z
UID:1915-1654992000-1655078399@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:በዓለ ጲራቅሊጦስ
DESCRIPTION:በዓለ ጲራቅሊጦስ  ከትንሳኤ በኋላ በሃምሳኛ ቀን የምናከብረው የመንፈስ ቅዱስ በዐል ነው።
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%88-%e1%8c%b2%e1%88%ab%e1%89%85%e1%88%8a%e1%8c%a6%e1%88%b5/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220602
DTEND;VALUE=DATE:20220603
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20220330T103703Z
LAST-MODIFIED:20220330T103703Z
UID:1913-1654128000-1654214399@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ዕርገት
DESCRIPTION:ዕርገት  ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የምድር ላይ ስራውን ያጠናቀቀበትና ያረገበት በዓል ነው።
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8b%95%e1%88%ad%e1%8c%88%e1%89%b5/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220417
DTEND;VALUE=DATE:20220418
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20260405T191957Z
LAST-MODIFIED:20260311T154519Z
UID:1831-1650153600-1650239999@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ሆሳዕና
DESCRIPTION:አስቀድሞ በቅዱስ መጽሐፍ በነቢዩ ዘካርያስ ‹‹ለጽዮን ልጅ እነሆ ንጉሥሽ የዋህ ሆኖ በአህያ ላይና በአህያይቱ ግልገል በውርንጭላይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል በሏት›› ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ይህ ሆነ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በአህያ ውርንጭላ ላይ ሆኖ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። (ዘካ.፱፥፱) \nቅዱስ ማቴዎስ እንደጻፈው ጌታችን ኢየሱስ በአህያ ላይ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም በቀረበ ጊዜ ሕዝቡ ተናወጠ። ሰዎች ሁሉ እርሱ በሚያልፍበት መንገድ ልብሳቸውን፣ የዘንባባ፣ የወይራና የዛፍ ቅርንጫፎች በማንጠፍ ለክብር ጌታ ምስጋናን፣ ውዳሴን አቀረቡለት። በመቅደስም ሳለ ሕፃናቱ ‹‹ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፣ ሆሣዕና በአርያም!›› እያሉ በታላቅ ድምጽ እየጮኹ አመሰገኑት። ‹‹ሆሣዕና … ሆሣዕና… ሆሣዕና በአርያም! በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ብሩክ ነው!›› እያሉ በአናታቸው ጀርባና እቅፍ ያሉ ሕፃናትና የቢታንያ ድንጋዮች ሁሉ ሳይቀሩ በታላቅ ደስታና ሐሴት ሆነው መድኃኒት፣ አዳኝና ቤዛ ለሆነው ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአንድ ድምፅ በንጹሕ አንደበት ዘመሩለት፤ አመሰገኑት። ምድርምና ሞላዋ፣ ውቅያኖሶች፣ ባሕሮችና ተራሮች፣ ሰማይ፣ ሰማየ ሰማያት፣ ከሰማይም በላይ ያለ ሰማይ፣ የእግዚአብሔር ፍጥረታት ሁሉ በዚህ ልዩ የሕፃናት የምስጋና ጥዑም ዜማ ተሞሉ፣ በደስታም እንደ እንቦሳ ዘለሉ። \nበዚህ ልዩ ሰማያዊ ቅኔ የሰማይ ሠራዊት፡- መላእክት፣ ሊቃናት፣ አጋእዝትና መናብርት ሁሉ በአንድነት በሐሴትና በደስታ ታደሙ። በዚህ ታላቅ የምስጋና፣ የፍቅር ዜማ ምድርም በሐሴትና በደስታ ተናወጠች። የፍቅር አምላክ፣ የሰማይና የምድር ሁሉ ፈጣሪ ዝቅ ብሎ፣ የዋህና ትሑትም ሆኖ በአህያ ውርንጫ ላይ ሆኖ መጥቷልና። \nሆሣዕና ጌታችን ከዚህ ቀን በኋላ ለሚያደርገው ገቢረ ተአምራት እና የሚቀበለው መከራ የሞት ጽዋ በመሆኑ ይህ ምስጋና የጌታንን የሞት ዕለት መቅረብ የሚያበስር ዐዋጅ ነበር፡፡ በዕለተ ሆሣዕና ሕፃናት፣ የተከተሉት ሕዝቡ ሁሉ በደስታ ሲዘምሩና ሲያመሰግኑ፣ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የሕዝበ እስራኤል በበደልና ኃጢአት ለኢየሩሳሌም ከተማ የመጥፋትና የመፍረስ ምክንያት እንደሚሆን ዐውቆና ጊዜውንም አሻግሮ አይቶ አለቀሰላት፤ ይህንንም ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ሲገልጽ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹ለሰላምሽ የሚሆነውን በዚህ ቀን አንቺስ ብታውቂ አሁን ግን ከዓይንሽ ተሠውሯል፡፡›› (ሉቃ.፲፱፥፵፪) \nስለዚህም በዚህ ቀን አምላካችን ጌታችንና ኢየሱስ ክርስቶስ የዋህና ትሑት በመሆን ራሱን ዝቅ አድርጎ ለሰው ልጆች ሁሉ ፍቅርን እንዳሳየ እንዲሁም ሰላምን እንዳበሠረ ሁሉ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ ለሰው ልጆች ሰላምን የምንሻና ፍቅርን በተግባር የምንገልጽበት መልካም የምስጋናና የውዳሴ ዕለት ነው፡፡ \nሆሣዕና በአርያም!!!
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%88%86%e1%88%b3%e1%8b%95%e1%8a%93/
ATTACH;FMTTYPE=image/png:https://www.baltimoreselassie.org/wp-content/uploads/2022/01/hosaena.png
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220327
DTEND;VALUE=DATE:20220328
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20220113T185201Z
LAST-MODIFIED:20220113T185201Z
UID:1829-1648339200-1648425599@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ደብረ ዘይት
DESCRIPTION:
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8b%b0%e1%89%a5%e1%88%a8-%e1%8b%98%e1%8b%ad%e1%89%b5/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220221
DTEND;VALUE=DATE:20220222
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20220113T185032Z
LAST-MODIFIED:20220113T185139Z
UID:1827-1645401600-1645487999@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ዓብይ ጾም
DESCRIPTION:
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8b%93%e1%89%a5%e1%8b%ad-%e1%8c%be%e1%88%9d/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220214
DTEND;VALUE=DATE:20220215
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20220113T183842Z
LAST-MODIFIED:20220113T183842Z
UID:1822-1644796800-1644883199@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ጾመ ነነዌ
DESCRIPTION:
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8c%be%e1%88%98-%e1%8a%90%e1%8a%90%e1%8b%8c/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220119
DTEND;VALUE=DATE:20220120
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210817T145439Z
LAST-MODIFIED:20220113T193608Z
UID:1804-1642550400-1642636799@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ጥር - (፲፩)/11 2014 ጥምቀት
DESCRIPTION:
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8c%a5%e1%88%9d%e1%89%80%e1%89%b5/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20220107
DTEND;VALUE=DATE:20220108
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210817T145305Z
LAST-MODIFIED:20210817T145340Z
UID:1802-1641513600-1641599999@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ልድት
DESCRIPTION:
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%88%8d%e1%8b%b5%e1%89%b5/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20211124
DTEND;VALUE=DATE:20211125
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210817T145100Z
LAST-MODIFIED:20210817T145236Z
UID:1798-1637712000-1637798399@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ጾመ ነብያት
DESCRIPTION: 
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8c%be%e1%88%98-%e1%8a%90%e1%89%a5%e1%8b%ab%e1%89%b5/
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20210927
DTEND;VALUE=DATE:20210928
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210804T155316Z
LAST-MODIFIED:20210810T113515Z
UID:1770-1632700800-1632787199@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:የመስቀል በዓል
DESCRIPTION:
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8b%a8%e1%88%98%e1%88%b5%e1%89%80%e1%88%8d-%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%8d/
ATTACH;FMTTYPE=image/jpeg:https://www.baltimoreselassie.org/wp-content/uploads/2021/08/Meskel.jpg
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20210911
DTEND;VALUE=DATE:20210912
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210723T175700Z
LAST-MODIFIED:20210804T155203Z
UID:1733-1631318400-1631404799@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ቅዱስ ዮሐንስ (እንቁጣጣሽ፤ የዘመን መለወጫ)
DESCRIPTION:History of Ethiopian New Year\nThe Ethiopian calendar is a solar calendar based on the Egyptian and Julian calendars and was brought to Ethiopia by missionaries. The year consists of 12 months of 30 days and a thirteenth month of five or six timekeeping days. \nPagume\, the 13th month in the Ethiopian calendar\, comes from the Greek word epagomene\, which means ‘days forgotten when a year is calculated’. This month has five days or six days in a leap year. According to the Ethiopian calendar\, a year has 365 days\, six hours\, two minutes and 24 seconds. Once every four years\, the six hours add up to 24 hours and become the sixth day in a leap year. Once in 600 years\, the two minutes and 24 seconds add up to a full day and form a seventh day. \n  \nBased on the Julian calendar basis\, the Ethiopian calendar is currently seven years and eight months behind the Gregorian calendar used in most of the world. \nEnkutatash means the ‘gift of jewels’. It is said to refer to the Queen of Sheba returning from her visit to King Solomon in Jerusalem in 980 BC. On the Queen’s arrival back in Ethiopia\, her chiefs welcomed her by filling her treasury with jewels (‘enku’). It may also refer to the countryside\, as this time of year coincides with the end of the rainy season meaning the landscape is covered with Adey Abeba\, whose bright yellow flowers appear almost in celebration of the impending harvest. \nCelebrations for the Ethiopian New Year usually last for a week and are focused on family events. The holiday starts on New Year’s Eve\, when each household light wooden torches called “chibo” in Amharic language\, that symbolise the coming of the new season of sunshine after the end of the rainy season that has prevailed since June. \nEnkuan Aderesachihu! (Happy New Year)
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%89%85%e1%8b%b1%e1%88%b5-%e1%8b%ae%e1%88%90%e1%8a%95%e1%88%b5/
ATTACH;FMTTYPE=image/png:https://www.baltimoreselassie.org/wp-content/uploads/2021/07/enkutatash.png
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;VALUE=DATE:20210807
DTEND;VALUE=DATE:20210808
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210628T173806Z
LAST-MODIFIED:20210804T154757Z
UID:1627-1628294400-1628380799@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:ጾመ ፍልሰታ
DESCRIPTION:ነሐሴ ፩ \nእመቤታችን ከአባቷ ከኢያቄም እና ከናቷ ከሐና ነሐሴ ፯ ቀን ተፀንሳ ግንቦት ፩ ቀን በሊባኖስ ተወልዳለች። <እምሊባኖስ ትወጽዕ መርአት ፦ ከሊባኖስ ሙሽራ ትወጣለች > እንደተባለ ። እመቤታችን በእናት አባቷ ቤት ሦስት ዓመት፤ በቤተ መቅደስ አሥራ ኹለት ዓመት፤ ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ፡ ከዮሐንስ ወልደዘብዴዎስ ዘንድ አሥራ አራት ዓመት ከዘጠኝ ወር ቆይታ በ ፷፬ ዓመት ዕድሜዋ በ፵፱ ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች። የእመቤታችንን ስም የሚገልጹ የውዳሴ ጽሑፎችም በዕድሜዋ ልክ ተደርሰዋል። ለምሳሌ የውዳሴ ማርያም ቁጥር ፷፬ ነው፤ የመልክዐ ማርያም ቁጥርም ፷፬ ነው።[1] \nባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ተሰባስበው አስከሬኗን ይዘው ወደ ጌቴሴማኒ መቃብር ለማሳረፍ ሲሄዱ አይሁድ ለተንኮል አያርፉምና ተተናኮሏቸው። ቀድሞ ልጇ ሞቶ ተነሣ፣ ዐረገ እያሉ ሲያስቸግሩን ይኖራሉ: ደግሞ አሁን እሷም ተነሣች፣ ዐረገች ሊሉ አይደል በማለት አይሁድ ተሰባስበው አስከሬኗን ለማቃጠል ሲተናኮሉ እግዚአብሔር በተአምር ከነዚያ አይሁዶች አድኗቸዋል ። የእመቤታችንንም አስከሬን ነጥቆ ከሐዋርያው ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር በገነት በዕፀ ሕይወት ሥር አኑሮታል። ከዚያ በኋላ ሐዋርያት ሥጋዋን አግኝተው ይቀብሩት ዘንድ በዐረፈች በስምንተኛው ወር ከነሐሴ ፩ ጀምሮ እስከ ነሐሴ ፲፬ ቀን ድረስ ኹለት ሱባዔ ይዘው በአሥራ አራተኛው ቀን ሥጋዋን ከጌታ ተቀብለው በጸሎትና በምህላ በፍጹም ደስታ በጌቴሰማኔ አሳረፉት ። በሦስተኛውም ቀን ተነሥታ ስታርግ ከሰኡቃዊያን ወገን የሆነው ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስ አያት። እርሱም በቀብር ሥርዓቱ ጊዜም አልነበረም። ሀገረ ስብከቱ ህንድ ስለነበር ሊያስተምር ወደዛው ሂዶ ነበርና። በዚያም ሲያስተምር ሰንብቶ በደመና ተጭኖ ሲመጣ ያገኛታል። ትንሣኤዋን ከርሱ ሰውራ ያደረገች መስሎት አዝኖ «ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀርቼ ነውን ?» ብሎ ቢያዝንባት እመቤታችንም ከርሱ በቀር ማንም ትንሣኤዋን እንዳላየ ነግራ አጽናናችው። ለሌሎቹ ሐዋርያትም እንዲነግራቸው ለምልክትም /ለምስክርም እንዲሆነው ሰበኗን /መግነዟን ሰጥታው ዐረገች። ቶማስም ኢየሩሳሌም ደርሶ ሐዋርያትን «የእመቤታችን ነገርስ እንደምን ሆነ?» ሲል ቢጠይቅ «አግኝተን ቀበርናት እኮ» አሉት። እርሱ ምስጢሩን አዉቆ ደብቆ «ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር» እንዴት ይሆናል ? አይደረግም ይላቸዋል። ሊያሳያቸውም መቃብሩ ዘንድ ሂደው ቢከፍቱት አጧት። እርሱም «አታምኑኝም ብዬ እንጂ እርሷስ ተነሥታ ዐርጋለች» በማለት ኹኔታውን ተረከላቸውና ለምስክር ይሁንህ ብላ የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው። ከዚህ በኋላ ለበረከት ይሆናቸው ዘንድ ሰበኑን ተካፍለው ወደየአህጉረ ስብከታቸው ሄዱ። ዛሬ በቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ በሚይዘው የመጾር መስቀል ላይ በሁለት ቀዳዳዎች አልፎ ተጠምጥሞ የምናየው መቀነት መሰል ጨርቅ የዚያ ሰበን ምሳሌ ነው። \nበዓመቱ ሐዋርያት ከያሉበት ተሰባስበው ቶማስ ትንሣኤሽን አይቶ እኛስ እንዴት ይቀርብናል ብለው ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምርው ሱባዔ ቢይዙ ከኹለት ሱባዔ በኋላ እንደገና ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ለማየት በቅተዋል። ሐዋርያዊት የሆነች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናም ምእመኖቿ ከእመቤታችን በረከትን እንዲያገኙ ይጾሙ ዘንድ ይህን ሐዋርያት የጾሙትን ጾም እንዲጾሙ ዐዉጃለች። ምእመናንም በተለየ መልኩ በጾም በጸሎት በሱባዔ ጽሙድ ሆነው ይህን ወቅት ያሳልፋሉ። \nየእመቤታችን ትንሣኤ ድንገት እንደእንግዳ ደራሽ እንደ ውሃ ፈሳሽ የተደረገ ሳይሆን በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት የተገለጸ ነው። ነቢዩ ዳዊት በመዝሙር ፻፴፩ ቁጥር ፲ ላይ «አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» ይላል። በዚህም ምእመናንን ወደ ምታሳርፍበት ወደ መንግሥተ ሰማያት የመቅደስህ ታቦት ድንግል ማርያምን ይዘህ ተነሥ አለ። ታቦት የጽላት ማደርያ እንደሆነ ሁሉ እመቤታችንም ለክርስቶስ ማደርያ በመሆኗ አማናዊት ታቦት ትባላለች። \nንጉሥ ሰሎሞንም በመኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ምዕራፍ ፪ ቁጥር ፲ ላይ «ውዴ እንዲህ ብሎ ተናገረኝ፤ ወዳጄ ሆይ ተነሽ፡ ውበቴ ሆይ ነይ» ብሏል። እዚህ ላይ «ወዳጄ …ውበቴ»” የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት ። ክቡር ዳዊት መዝሙር ፵፬ ቁጥር ፱ ላይ «በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች» እንደሚል ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛነቱን ከፈጸመ በኋላ ወደ ቀደመ ክብሩ እንዳረገ እመቤታችን ቅድስት ድንገል ማርያምም በቀኙ ትቀመጥ ዘንድ «ተነሽ ነይ» አላት ። እንግዲህ ይህንና የመሰለዉን ሁሉ ይዘን የእናታችንን ዕረፍቷንና ትንሣኤዋን እንዘክራለን እንመሰክራለንም።
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8c%be%e1%88%98-%e1%8d%8d%e1%88%8d%e1%88%b0%e1%89%b3/
ATTACH;FMTTYPE=image/jpeg:https://www.baltimoreselassie.org/wp-content/uploads/2021/06/The_Apostles_Witness_the_Assumption_of_Saint_Mary.jpg
END:VEVENT
BEGIN:VEVENT
DTSTART;TZID=America/New_York:20210714T040000
DTEND;TZID=America/New_York:20210714T120000
DTSTAMP:20260409T162746
CREATED:20210624T200643Z
LAST-MODIFIED:20210702T171438Z
UID:1550-1626235200-1626264000@www.baltimoreselassie.org
SUMMARY:አመታዊ በዓለ ንግሥ
DESCRIPTION:ኪዳን የሚለው ቃል “ቃል” ከሚለው ጋር እየተዛረፈ በብሉይ ኪዳን ለ280 ጊዜ ያህል ሲጠቀስ በአዲሰ ኪዳን ደግሞ ከ32 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል፡፡ “ኪዳን” ቃሉ “ተካየደ” ተማማለ፣ ቃል ተገባባ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡፡ “ምሕረት” የሚለው ቃል ደግሞ ማብራሪያ ሳያሻው ምሥጢሩ ከነዘይቤው ከግእዝ የተወረሰ ነው፡፡
URL:https://www.baltimoreselassie.org/event/%e1%8a%a0%e1%88%98%e1%89%b3%e1%8b%8a-%e1%8a%95%e1%8c%8d%e1%88%b0-%e1%89%a0%e1%8b%93%e1%88%8d/
ATTACH;FMTTYPE=image/jpeg:https://www.baltimoreselassie.org/wp-content/uploads/2021/06/maxresdefault.jpg
END:VEVENT
END:VCALENDAR